tg-me.com/nibab_lehiwot/165
Last Update:
የእኔ ታሪክ(ምዕራፍ- 2)
ክፍል 8
ሕዝቅኤል እና ቪቪያን የናፍቆታቸውን ከተቃቀፉ እና ከተላቀሱ በኋላ ተቀምጠው መወያየት ጀመሩ። ሕዝቅኤልም ምንም እንኳን ውስጡ ባያምንበትም የፈለግሽውን አድርጊ እኔ ፈቅጄልሻለሁ ብቻ ግን ተጠንቀቂ የማይሆን ነገር እንዳታደርጊ ልትመከሪ የሚገባ አይነት ልጅ እንዳልሆንሽ አውቃለሁ ግን በእድሜ ከአንቺ ስለምበልጥ ስለ ህይወት ከአንቺ የተሻለ አውቃለሁ። ያየሁትን ሁሉ ነግሬሻለሁ አሁን እንደምታስቢው ቀላል እንደማይሆን እወቂው ግን አንዴ ሜዳ ውስጥ እስከገባሽ ድረስ ማሸነፍ እንጅ ወደ ኋላ ማፈግፈግ የለብሽም መንገድሽን ያሳምርልሽ ልጄ። ቪቪያን ቅስም የሚሰብር ንግግሩ ውስጧን አሳመማት ምን ያክል ቢወዳት እንደሆነ ይሄንን እያደረገ ያለው ከምን ጊዜውም በላይ ዛሬ ወለል ብሎ ታያት። ምንም ሳትለው እጁን ብቻ ስማው ወደውስጥ ገባች።
እንደ እውነቱ ከሆነ አሌፍን ምንም ያክል ብትወደውም ግንኙነት ለመጀመር ግን መጀመሪያ የአባቷ ፈቃደኝነት እንደሚያስፈልጋት ነግራው መልሷን እየጠበቀ ነበር። ቪቪያን ግን ለ አባቷ አሌፍ ፍቅረኛዋ እንደሆነ አድርጋ ነበር የነገረችው። ይሔንንም ያደረገችው ሆን ብላ ነበር።
ወደክፍሏ እንደገባች በደስታ እየፈነጠዘች ለ አሌፍ ደወለች። ሄሎ ቪ....አላት ዝምተኛው አሌፍ አባዬኮ እሽ አለ አለችው ሰላም እንኳን ሳትለው። አሌፍ ግን እንዳሰበችው ያን ያክል ደስተኛ አልሆነም። አይ ደስ ይላል ሰሞኑን እንገናኝና እናወራለን ሰላም ሁኝ ብሏት ስልጉን ዘጋው። ቪቪያን ግራ ገባት እውነት ግን አሌፍን መምረጤ ትክክለኛ ውሳኔ ነው ? ስትል ለራሷ አጉረመረመች።
አሌፍ ሻይ እየጠጣ ነበር ቀድሞ የጠበቃት። እንደደረሰች ሰላም ብላው ተቀመጠች። ደህና ነህ አይደል አለችው ፈገግ እያለች። አወ ቪ አሁን ጊዜ የለኝም ስሚኝ አብረን መሆን አንችልም ይሔንን ልነግርሽ ነው የመጣሁት በጣም ይቅርታ ቪቪያን።
ለምን ????
አለችው ግራ በተጋባ አስተያየት እያየችው።
የሰማሁት ታሪክ ስላለ ሕይወት እኛ እንዳሰብነው ቀላል ስለማይሆን.....
ጥሩ ጓደኞች እንሆናለን ደህና ሁኝ ብሎ ግንባሯን ስሟት ተነስቶ ወጣ።
ቪቪያን በፀጥታ ወደ ቤቷ ተራመደች ሀዘኗ ፊቷ ላይ በግልጽ ቢታይም ግን ላለማልቀስ ከራሷ ጋ እየታገለች ነው። በሩን ከፍታ ስትገባ እንደተለመደው ሕዝቅኤል በረንዳ ላይ ተቀምጦ መፅሐፉን እያነበበ ነበር። አባ የመጨረሻ ጥያቄ ላስቸግርህ እባክህ አለችው ከይኖቿ ሊወጡ የሚያቆጠቁጡ እንባወቿን ወደ ውስጥ ለመመለስ እየታገለች።
ምንድን ነው ልጄ ግራ ገባው።
ወንድሜን ፈልጌ ላግኘው ወደዚያች ሀገር ላከኝ።
ቪቪያን ሕዝቅኤል ፍጥጥ ብሎ ጠራት።
አባየ ካልሆነ እሞታለሁ በቃ ወንድሜ ያስፈለሰገኛል። እንባወቿ ሕጓን ጥሰው ወደታች ተውረገረጉ......
ምን ሆነሻል???
ሕዝቅኤል ደነገጠ።
ይቀጥላል...........
@nibab_lehiwot
BY ሕይወትን - በገፅ
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/nibab_lehiwot/165